Tesfahiwot

shape የስም ስያሜ

የሰንበት ትምህርት ቤቱ ስያሜ

የወልቂጤ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን ተስፋ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት እየተባለ የሚጠራ ሲሆን ይህ የወ/ጤ/ደ/ብ/ቅ/ገ/ቤ/ክ ተስፋ ህይወት ሰ/ት/ቤት ስያሜው የፀደቀው በ2011ዓ.ም በደብሩ አስተዳዳሪ በመጋቤሐዲስ አባ ኤልያስ(ቆሞስ) ነው ፡፡ ይኸውም ሰ/ት/ቤቱ ለቤተክርስትያኑ ተስፋ መሆኑን ለማመልከት ነው ፡፡

አባላት
0 +

ስለ ሰንበት ት/ቤቱ መሰረታዊ መረጃዎች

July 5
የሰንበት ትምህርት ቤቱ ራዕይ

ሰንበት ትምህርት ቤቱ 2022 ዓ.ም በኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ከሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በትምህርት አሰጣጥ እና በአባላት ስነ ምግባር በግንባር ቀደምነት የሚጠቀስ ሰንበት ትምህርት ቤት ሆኖ ማየት ።  

January 31
የሰ/ት/ቤቱ ተልዕኮ
(ያዘዝኋችኹንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራቿኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤)ማቴ 28•20

- በአጥቢያው የሚገኙ ወጣቶች እና ህፃናት ትክክለኛውን ትምህርተ ሃይማኖት እና የአብነት ትምህርትን በማስተማር የቤተክርስትያኗን ዶግማ ፣ትውፊት ፣ ቀኖና ፣ ስርአት እና ታሪክ እንዲያውቁ ማድረግ፡፡

- የሰ/ት/ቤቱ አባላት በመናፍቃን እንዳይነጠቁ አስፈላጊውን እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ፡፡

- የተለያዩ መንፈሳዊ ጉባዬዎችን በማዘጋጀት ለምዕመኑ ቃለ እግዚአብሔርን ማስተማር ፡፡

- በቤተክርስቲያኑ ውስጥ በሚደረጉ ልዩ ልዩ መርሀ ግብራት ላይ በመሳተፍ የቤተክርስቲያኑን አገልግሎት ማገዝ ፡፡

- አባላቱ በሰ/ት/ቤቱ ውስጥ ባሉ ክፍላት ላይ በመሳተፍ መክሊታቸውን እንዲያተርፉበት ማድረግ፡፡

- ሕፃናት እና ወጣቶችን የቤተክርስትያንን ሚስጥራትን በማስተማር የሚስጢር ተሳታፊ እንዲሆኑ ማስቻል።

February 2
የሰንበት ት/ት ቤቱ ዓላማ

-  መንፈሳዊ ወጣቶች እና ህፃናት የቤተክርስትያንን እና የሀገርን ታሪክ በሚገባ አውቀው በነገረ
መለኮት ሃይማኖታዊ ትምህርቶችን ተምረው የነገዋን ቤተክትስትያን እና ሀገርን በሃላፊነት ለመረከብ
ብቁዎች ማድረግ ፡፡

- ከስብከተ ወንጌል ፣ ከካህናት እና ከተለያዩ አባላት ጋር ተባብሮ በመስራት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ
ሃይማኖት ፣ ስርአት እና ትውፊት ሳይበረዝ እና ሳይለወጥ ከተውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ
ማድረግ ፡፡

-  የሰ/ት/ቤቱ አባላት ያላቸውን መክሊት (ፀጋ) ተጠቅመው ቤተክርስትያንን እንዲያገለግሉ ማድረግ

- ወጣቶች እና ህፃናት የሃይማኖታቸውን ስርአት ፣ ትውፊት እና ዶግማ እንዲያውቁ ፤በስነምግባራቸውም የታነጹ እና ክርስትያናዊ ግብረገብ የተላበሱ እንዲሆኑ ማድረግ ፡፡

- ሃይማኖታቸውን አፅንተው እንዲይዙና እንዲጠብቁ ማድረግ ፡፡ 2ኛ ጢሞ 4፥7-8 "ሃይማኖቴን
ጠብቄአለሁ ወደ ፊት የፅድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል "

shape ዜና ቤተ ክርስቲያን

የመምህራን ግንዛቤ ማስጨበጫና የትምህርት ማስጀመሪያ ውይይት

በወልቂጤ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ተስፋ ሕይወት ሰ/ት/ቤት የመምህራን ግንዛቤ ማስጨበጫና የትምህርት ማስጀመሪያ ውይይት መስከረም 27/2018 ዓ.ም ተከናወነ። መ/ር ሳሙኤል ...

የ2018 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል

የመስቀል ደመራ በዓል በወልቂጤ ከተማ  በድምቀት ተከበረ። ...

ተስፋሕይወት ሰንበት ት/ቤትሽ በአንቺ ትኮራለች!

የሰንበት ት/ቤታችን የ12ኛ ክፍል አባል ተማሪ ሄላ ፈለቀ በዘንድሮው ሀገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና 546 ከፍተኛ ውጤት በማምጣትሽ እንኳን ደስ ...

የአዲስ ዓመት በዓል በተስፋሕይወት ሰ/ት/ቤት በድምቀት ተከበረ።

የ2018 አዲስ ዓመት የበዓል ልዩ መርሃግብር እሁድ መስከረም 04 2018 ዓ.ም ተካሄዷል። በመርሃግብሩ የተለያዩ የበዓል መርሃግብራት የቀረቡ ሲሆን የደብራችን አስተዳዳሪ ...
Loading...
shape ወቅታዊ ጉዳዮች

እጅግ አሳዛኝና ልብ የሚሰብር ኀዘን!!

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ወረዳ አረርቲ ደብረ ገነት ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያ ላይ በአለው አዲሱ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለውስጥ ሥዕል ...

የመነኮሳት ግድያ

በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ቁጥራቸው ያልታወቀ በዋሻ የሚኖሩ መነኮሳት በታጣቂዎች ተገደሉ። በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ...

ቅድስት አፎምያና ባሕራን

ዲያቆን ተስፋዬ ቻይሰኔ ፲፩፤፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐዋጅ ታውጀው ከሚጾሙ አጽዋማት አንዱ የሆነው ...

“ቃል ሥጋ ሆነ” (ዮሐ. ፩፥፲፬/1፥14)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ እንኳን ለጌታችን፣ ለአምላካችን እና ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ። ይህ ቃልሥጋየመኾን ምስጢር፡- እግዚአብሔር ወልድ በተለየ ...
error: