የተስፋሕይወት ሰንበት ት/ቤት 28ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ከታህሳስ 24 – የካቲት 82018 ዓ.ም በተለያዩ መርሃግብራት እንደሚከበር ተገለጸ። የምሥረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በተሰናዱ ልዩ ልዩ መርሃግብራት የሚከበር ሲሆን የመርሃግብራቱ ዝርዝርም በዛሬው ዕለት ይፋ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት፡-
👉 ከታህሳስ 24 – 26 መንፈሳዊ አውደ ርዕይ – “ክብረ ክህነት”ን በተመለከተ።
👉 ጥር 2 (ጥናታዊ ጽሑፍ) – የወልቂጤ/ደ/ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የተስፋ ሕይወት ሰንበት ት/ት ቤት የአባላትን አገልግሎት ለማሳደግ የተደረገ የትግበራ ጥናት በሰንበት ት/ቤቱ ጥናትና ምርምር ክፍል ይቀርባል።
👉 ጥር 17 – የወላጆች ጉባኤ :- ወላጆች የልጆቻቸውን ሰ/ት/ቤት ምሥረታ በልዩ ልዩ መርሃግብራት የሚያከብሩበት።
👉 የካቲት 1 – የአባላት ጉዞ
👉 የካቲት 8 – የአባላትጉባኤ :- ነባርና አዳዲስ አባላት የሚተዋወቁበት፣ የሰንበት ት/ቤቱ ታሪክ የሚዘከርበትና የምሥረታው የማጠቃለያ ልዩ መርሃግብር።
በእነዚህ ምዕመናንን እንዲሁም አባላትን በሚያሳትፉ መርሃግብራት ከታህሳስ24እስከየካቲት8 ድረስ አብረውን እንዲያከብሩ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።




